በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ ያለውን የአረንጓዴ አሻራ ‹‹አሻራችን ለትውልዳችን›› መርሃ ግብርን ተከትሎ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን አመራር እና ሰራተኞች ነሐሴ 2 ቀን 2014 ዓ.ም በሞጆ ሎጅስቲክስ ማዕከል ግንባታ አካባቢ 2ኛውና ማጠቃለያውን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡

በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ያብባል አዲስ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ በባለስልጣን መ/ቤቱ ብቻ ለ2ኛ ጊዜና በማጠቃለያ የተካሄደ ችግኝ ተከላ መሆኑን በመጠቆም ችግኝ መትከል የጎርፍ አደጋን ለመከላከል፣ የሙቀት አማቂነትን በመቀነስ፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው በተመሳሳይ መልኩ በወንዶገነት፣ በሎሜ ወረዳና በሞጆ አካባቢ ከተለያዩ መ/ቤቶች ጋር በመተባበር በርካታ ችግኞችን መትከል መቻሉን አስታውሰው፣ በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉ የባለሥልጣኑ እና የሞጆ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አመራርና ሰራተኞች፣ የፕሮጀክቱ ኮንትራክተር እና አማካሪ ድርጅት አመራርና ሰራተኞች ላደረጉት ተሳትፎ አመስግነዋል፡፡
በ2ኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ 2ሺ ችግኞች መተከላቸውን እንዲሁም በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን፣ የፕሮጀክት ጽ/ቤት፣ የሎጅስቲክስ ትራንስፎርሜሽን ጽ/ቤት፣ የፕሮጀክቱ አማካሪና ኮንትራክተር አመራርና ሰራተኞች ተሳታፊ መሆናቸው የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ ብርሃን ኪዳኔ ገልፀዋል፡፡

ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎን የሞጆ ሎጅስቲክስ ማዕከል ግንባታ ያለበትን ደረጃ አስመልክቶ የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስተባባሪው አቶ ደሳለኝ ጌታሁን ዝርዝር ገለፃ በማቅረብ ተሳታፊዎች እንዲጎበኙ የተደረገ ሲሆን የግንባታ ሥራው ከኮንትራክተርና አማካሪ ድርጅቱ ጋር በቅርበት በመመካከር በተሻለ ደረጃ እየተከናወነ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ የማጠቃለያ ፕሮግራሙ በሞጆ ማዕከል ግንባታ መከናወኑ ለአረንጓዴ ሎጅስቲክስ የበኩሉን ሚና የሚያበረክት በመሆኑ ለመትከል የተደረገውን ርብርብ በመንከባከብ ሊደገም ይገባዋል፡፡

Some Useful links
Tags Cloud
Latest Posts
- በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል አምራቾች የሚያነሷቸውን ችግሮች መሰረት ያደረገ ዘላቂ ስራ መስራት ያስፈልጋል /አምባሳደር ግርማ ብሩ/
- መንግሥት የሎጂስቲክስ ዘርፉን በማዘመን የገቢና የወጪ ንግድን ቀልጣፋ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው::
- ሁለተኛው ምዕራፍ የሎጂስቲክ ማስተር ኘላን የጥናት ሪፓርት በባለድርሻ አካላት ተገመገመ::
- የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን በEQA ባለሙያዎች የተካሄደውን የጥራት ግምገማ በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ::
- የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የማኔጅመንት አባላት የማሪታይም እና ሎጂስቲክስ ማኔጅመንት ሲስተም ( MLMS) (Inception Report) ገመገመ::











Leave a Reply