የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ 42 ኦፊሰሮችን አስመረቀ፤

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አካዳሚ የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ በኢንጂን እና በዴክ ኦፊሰርነት ያሰለጠናቸውን 42 ባሕረኞች በጥር 09 ቀን 2016 ዓ.ም. አስመርቋል፡፡

ጥር 9 ቀን 2016 ዓ.ም የተመረቁት ባሕረኞች የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ስልጠናዎችን በብቃት ያጠናቀቁ 18 የኢንጂን እና 24 የዴክ በአጠቃላይ 42 ኦፊሰሮች መሆናቸው ተገልጿል።

በምረቃት ሥነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን   ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን  ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
Source: EMA Telegram Channel Jan, 19 2024

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *