April 27, 2024
የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ 42 ኦፊሰሮችን አስመረቀ፤

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አካዳሚ የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ በኢንጂን እና በዴክ ኦፊሰርነት ያሰለጠናቸውን 42 ባሕረኞች በጥር 09 ቀን 2016 ዓ.ም. አስመርቋል፡፡

ጥር 9 ቀን 2016 ዓ.ም የተመረቁት ባሕረኞች የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ስልጠናዎችን በብቃት ያጠናቀቁ 18 የኢንጂን እና 24 የዴክ በአጠቃላይ 42 ኦፊሰሮች መሆናቸው ተገልጿል።

በምረቃት ሥነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን   ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን  ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
Source: EMA Telegram Channel Jan, 19 2024

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *