April 15, 2024

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ከአውሮፓ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ ማሪታይም ድርጅት ጋር በመተባበር ለማሪታይም ዘርፍ ባለድርሻ አካላት በዓለም አቀፍ የማሪታይም ሕግጋት ላይ ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 4 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ የመርከብ ባለቤት ሀገር ከመሆኗም ባሻገር የዓለም አቀፍ የማሪታይም /የባህር ዘርፍ በመጠቀም ከ85 በመቶ በላይ ንግዷን የምታሳልጠው እና ባህረኞችን በማሰልጠን በዓለም የመርከብ ድርጅቶች እንዲሰማሩ በማድረግ ዘርፉ ለሀገራዊ እድገት የበኩሉን ሚና እንዲጫዎት በማድረግ ላይ በመሆኗ በዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም አሟጦ ለመጠቀም ባለድርሻ አካላትን ማሰልጠንና የሚጠበቅባቸውን ድርሻ እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን በስልጠናው ተብራርቷል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *