
አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወደብ፣ ተርሚናልና ሎጂስቲክስ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማሞ ምህረቱ የተመራ እና የኢትዮጵያ ባህርና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሮባ መገርሳንና ሌሎች የስራ ሃላፊዎችን ያካተተ ልዑክ በሞሮኮ የስራ ጉብኝት አድርጓል፡፡
ልኡካን ቡድኑ የሞሮኮ ወደብ፣ ተርሚናልና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ላይ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
በጉብኝቱም ከሞሮኮ የወደብ፣ ተርሚናልና ሎጅስቲክስ ተቋም ሀላፊ መህዲ ታዚ ሪፊ ጋር በደረቅ ወደብ ልማትና አገልግሎት እንዲሁም የኢትዮጵያ ሎጂስቲክስ አገልግሎት ዘርፉን ለማሳደግ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረዋል።

ከውይይቱ መጠናቀቅ በኋላም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከሞሮኮው አቻ ተቋም ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በዘርፉ በትብብር መስራትና መዋዕለ ነዋይ ማፍሰስን የሚያጠቃልል ነው ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ የባህርና ሎጀጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ስር የሚገኘውን የቃሊቲ ደረቅ ወደብና ተርሚናል የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን የደረጃ ማሳደግን በጋራ መስራትን ያካተተ መሆኑን ከባህርና ትራንስፖርት ሎጀስቲክስ ድርጅት የተገኘው መረጃ አመላክቷል።
Some Useful links
Tags Cloud
There’s no content to show here yet.
Latest Posts
- የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የመሰረተ ልማት እና ትራንስፓርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስለተቋሙ የግንዛቤ ማሰጨበጫ መድረክ አደረገ::
- አማራጭ ወደቦችን ለመጠቀም የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ::
- የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ወቅታዊና የሎጂስቲክስ አቅምን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተገለጸ
- በመልቲ ሞዳል ትራንሰፖርት ኦፕሬተርነት መሳተፍ ለሚፈልጉ ድርጅቶች ለ 2ኛ ጊዜ የወጣ የጥሪ ማስታወቂያ
- Djibouti’s new port scheme excludes Ethiopia from the mix