
አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ሞሮኮ በወደብ፣ ተርሚናልና ሎጂስቲክስ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማሞ ምህረቱ የተመራ እና የኢትዮጵያ ባህርና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሮባ መገርሳንና ሌሎች የስራ ሃላፊዎችን ያካተተ ልዑክ በሞሮኮ የስራ ጉብኝት አድርጓል፡፡
ልኡካን ቡድኑ የሞሮኮ ወደብ፣ ተርሚናልና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ላይ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
በጉብኝቱም ከሞሮኮ የወደብ፣ ተርሚናልና ሎጅስቲክስ ተቋም ሀላፊ መህዲ ታዚ ሪፊ ጋር በደረቅ ወደብ ልማትና አገልግሎት እንዲሁም የኢትዮጵያ ሎጂስቲክስ አገልግሎት ዘርፉን ለማሳደግ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ዕድሎች ዙሪያ መክረዋል።

ከውይይቱ መጠናቀቅ በኋላም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከሞሮኮው አቻ ተቋም ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በዘርፉ በትብብር መስራትና መዋዕለ ነዋይ ማፍሰስን የሚያጠቃልል ነው ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ የባህርና ሎጀጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ስር የሚገኘውን የቃሊቲ ደረቅ ወደብና ተርሚናል የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን የደረጃ ማሳደግን በጋራ መስራትን ያካተተ መሆኑን ከባህርና ትራንስፖርት ሎጀስቲክስ ድርጅት የተገኘው መረጃ አመላክቷል።
Some Useful links
Tags Cloud
There’s no content to show here yet.
Latest Posts
- “የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ በሀገራችን ለተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት የአስቻይነት ሚናውን በሚገባ ተወጥቷል።” ክቡር ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ
- የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የISO 9001-2015 ሠርተፊኬሽን ለማግኘት በተሻለ ቁመናና ዝግጅት ላይ መሆኑ ተገለፀ
- በቀላሉ የሚበላሹ የግብርና ምርቶችን ማቆያ የቀዝቃዛ መጋዘንና ማጓጓዣ የአሠራር ሥርዓትን አስመልክቶ በተካሄደ ጥናት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ ፡፡
- የተቀናጀ የጭነት ትራንስፖርት አስተዳደር ስርዓት የምረቃ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
- የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና የሎጅስቲክስ አቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር የትምህርት እና ምርምር መርሀግብር የሚያካሂዱ ዩኒቨርስቲዎች የጋራ የምክክር መድረክ ተካሄደ።